ለደኅንነታቸው ሲባል ስማቸው እንዲገለጽ ያልፈቀዱ የአቶ በቴ ኡርጌሳ የቅርብ ጓደኛ ለቢቢሲ እንደተናገሩት አቶ በቴ በኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ ሸዋ ዞን በምትገኘው መቂ ከተማ የተገደሉት ትናንት ማክሰኞ ሚያዚያ 1/2016 ዓ.ም. እኩለ ሌሊት ላይ ነው።
ፓርቲያቸው የኦሮሞ ነጻነት ግንባር የፖለቲካ ኦፊሰሩን ግድያን በተመለከተ እስካሁን ያለው ነገር ባይኖርም የፓርቲው የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ለሚ ገመቹ በፌስቡክ ገጻቸው ላይ “በቴ የሆነውን ማመን አቅቶኛል” ሲሉ ጽፈዋል።
አቶ በቴ የካቲት አጋማሽ ላይ በቁጥጥር ስር ውለው ለሁለት ሳምንታት ያህል በእስር ከቆዩ በኋላ በ100 ሺህ ብር የገንዘብ ዋስትና የተለቀቁት ከአንድ ወር ገደማ በፊት የካቲት 30/2016 ዓ.ም. ነበር።
ቢቢሲ ያነጋገራቸው የፖለቲከኛው የቅርብ ጓደኛ እንደሚሉት፤ አቶ በቴ በመቂ ከተማ አርፈው ከነበረበት የሆቴል ክፍል ውስጥ እንዲወጡ ከተደረጉ በኋላ ተገድለው አስክሬናቸው መንገድ ላይ ተጥሎ ተገኝቷል።
የአቶ በቴ ኡርጌሳ ላይ ግድያውን ማን እንደፈጸመው እንደማያውቁ የገለጹት እኚህ ግለሰብ፤ በአሁኑ ወቅት በመቂ ከተማ የቴሌኮም አገልግሎት በመቋረጡ ተጨማሪ መረጃ ማግኘት አዳጋች እንደሆነባቸው ጨምረው ተናግረዋል።
Oromo Liberation Front (OLG) political officer Bete Urgesa was killed and his body was found in his home town of Meki.
A close friend of Mr. Bete Urgesa, who did not allow his name to be revealed for their safety, told the BBC that Mr. Bete was killed in Meki town in East Shewa Zone of the Oromia region on Tuesday, April 1, 2016. It’s midnight.
Although there is still no information regarding the killing of the political officer of the Oromo Freedom Front, the party’s public relations officer, Mr. Lemi Gemechu, wrote on his Facebook page, “I can’t believe what happened to me.”
Mr. Bete was arrested in mid-February and after two weeks in prison, he was released on a bail of 100,000 Birr about a month ago on February 30/2016. has been.
According to a close friend of the politician who was interviewed by the BBC; Ato Bete was killed after being forced out of the hotel room where he was staying in Meki City and his body was found dumped on the road.
This individual who stated that they do not know who committed the murder of Mr. Te Urgesa; They added that it is difficult for them to get more information due to the interruption of telecom services in Miki city.


Leave a comment