የምክር ቤቱ አፈጉባኤ አቶ ታገሰ ጫፎ እና የፍትህ ሚኒስትሩ ጌዲዮን ጢሞቲዮስ (ዶ/ር)

ላለፉት ስድስት ወራት በዋናነት በአማራ ክልል ላይ ተጥሎ የቆየው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ለተጨማሪ አራት ወራት እንዲራዘም የቀረበውን ሐሳብ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አጸደቀ።

ምክር ቤቱ ዛሬ አርብ ጥር 24/2016 ዓ.ም. ባካሄደው ልዩ ስብሰባ ሐምሌ 28/2015 ዓ.ም. የሕዝብን ሰላም እና ደኅንነት ለማስጠበቅ ያወጣውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ቁጥር 6/2015 ለማራዘም የቀረበለትን የውሳኔ ሐሳብ አጽድቋል።

በዛው ልዩ ስብሰባ የሕዝብ ተወካዮች ምክረ ቤት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ለተጨማሪ አራት ወራት እንዲራዘም በሁለት ተቃውሞ እና በሦስት ድምፀ ተአቅቦ በአብላጫ ድምፅ ወስኗል።

በሚቀጠለው ሳምንት መጀመሪያ ላይ የስድስት ወር ጊዜው የሚጠናቀቀውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅን ማራዘም ያስፈለው “ተጨማሪ ሥራዎች በመኖራቸው” እንደሆነ በዛሬው የምክር ቤቱ ስብሰባ ላይ መገለጹን ብሔራዊ የቴሌቪዥን ኢቲቪ ዘግቧል።

The Speaker of the Council Mr. Tagese Thafo and the Minister of Justice Gideon Timotios (Dr.)

The House of Representatives approved the proposal to extend the state of emergency, which has been imposed mainly on the Amhara region for another four months.

The Council today, Friday, January 24/2016. In the special meeting held on July 28/2015. He approved the proposal to extend the Emergency Proclamation No. 6/2015 issued to protect public peace and security.

In the same special meeting, the House of People’s Representatives decided by majority vote to extend the state of emergency for another four months with two dissenting votes and three abstentions.

National television ETV reports that the extension of the state of emergency, which expires at the beginning of next week, is necessary because of “more work to be done”.

Design a site like this with WordPress.com
Get started