አንድ ከፍተኛ የተባበሩት መንግሥታት ባለሥልጣን እስራኤል በራፋህ ላይ ለመፈጸም ያሰበችው ጥቃት ወደ “ጭፍጨፋ” ሊያመራ ይችላል ሲሉ አስጠነቀቁ።

የመንግሥታቱ ድርጅት የሰብዓዊ መብት ኃላፊ ማርቲን ግሪፊትስ፤ ጋዛ ያሉ ፍልስጤማውያን “ከዚህ በፊት ታይቶ በማይታወቅ መልኩ እየተሰቃዩ” ነው ብለዋል።

እስራኤል በራፋህ ላይ የምትፈጽመው ወረራ መዘዙ ብዙ ነው የሚሉት ባለሥልጣኑ ነገሮች “ከቁጥጥር ውጭ” ሊሆኑ እንደሚችሉ ያስጠነቅቃሉ።

የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤኒያሚን ኔታኒያሁ ራፋህ ተደብቀዋል ያሏቸውን የሐማስ ታጣቂዎች ለመደምሰስ ዝተዋል።

ከዚህ ቀደም ባልተለመደ መልኩ ጠንከር ያለ አስተያየት የሰጡት ግሪፊትስ ከአንድ ሚሊዮን በላይ ሰዎች “ራፋህ ውስጥ ታጉረው፤ ከሞት ጋር ተፋጠዋል” ብለዋል።

አክለውም በከተማዋ ያሉ ሰላማዊ ዜጎች ያላቸው የምግብ ክምችት አነስተኛ፤ የመድኃኒት አቅርቦቱም አሳሳቢ መሆኑን ገልጠዋል።

የተባበሩት መንግሥት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ቃል አቀባይ የሆኑት ስቴፋኒ ዱጃሪክ፤ እስራኤል ሰላማዊ ዜጎች ከራፋህ ስለሚወጡበት ሁኔታ ያወጣችው ዕቅድ አልደረሰንም ሲሉ ለቢቢሲ ተናግረዋል።

“የተባበሩት መንግሥት ሰዎች ተገደው ከመኖሪያ ቤታቸው ተፈናቅለው ሲወጡ ተባባሪ መሆን አይፈልግም” ብለዋል ቃል አቀባዩ።

A senior UN official has warned that an Israeli attack on Rafah could lead to “massacre”.

Martin Griffiths, Head of Human Rights of the Organization of the Nations; He said Palestinians in Gaza were “suffering like never before”.

Israel’s raid on Rafah has far-reaching consequences, the official warned, warning that things could get “out of control.”

Israeli Prime Minister Benjamin Netanyahu has threatened to wipe out Hamas militants who Rafah says are hiding.

Griffiths, who has made unusually strong comments in the past, has been followed by more than a million people, saying, “Brave it in your Rafah; They have faced death,” he said.

He added that civilians in the city have little food stock. They also revealed that the supply of medicine is a concern.

Stephanie Dujarric, spokeswoman for UN Secretary-General Antonio Guterres; They told the BBC that Israel has not received the plan for the evacuation of civilians from Rafah.

“The United Kingdom does not want to be an accomplice when people are forcibly displaced from their homes,” said the spokesman.

Design a site like this with WordPress.com
Get started