የታንዛንያው የነጻነት ታጋይ ጁሊየስ ኔሬሬ በአፍሪካ ኅብረት መቀመጫ አዲስ አበባ ሐውልት ቆመላቸው።

ጁሊየስ ኔሬሬ ታንዛንያ ወይም በቀድሞ አጠራሯ ታንጋኒካ ከብሪታንያ ቅኝ ግዛት ጭቆና እንድትላቀቅ ከፍተኛ ሚና የነበራቸው ታጋይ ነበሩ።

አገራቸው ነጻነቷን ከተቀዳጀችም በኋላ ኔሬሬ ከአውሮፓውያኑ 1961- 1985 ድረስ መርተዋል።

በስዋሂሊ ቋንቋ ምዋሊሙ (መምህር) በመባል የሚታወቁት ኔሬሬ በፓን አፍሪካኒዝም እሳቤ ላይ በነበራቸው ቁርጠኝነት ታሪክ ያወሳቸዋል።

በደቡብ አፍሪካ ጨቋኙን የነጮች አገዛዝ፣ ወይም አፓርታይድ በመባል የሚታወቀውን ሥርዓት ይታገሉ ለነበሩ የነጻነት ታጋዮችም በታንዛንያ እንዲጠለሉ አድርገዋል።

የአፍሪካ አንድነት ድርጅት ምስረታም ላይ ቁልፍ ሚና ከተጫወቱ መሪዎች አንዱ ናቸው።

የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ሙሳ ፋኪ ማሃማት በርካታ የአፍሪካ መሪዎች በተገኙበት ሥነ ስርዓት ላይ ሐውልቱን የመረቁ ሲሆን ለአህጉሪቷ ባደረጉት አስተዋጽኦም ከፍተኛ ምስጋናን ችረዋቸዋል።

በአውሮፓውያኑ 1963 የአፍሪካ አንድነት ድርጅት ሲመሰረት ኔሬሬ “አህጉራችን አንድ ናት። ሁላችንም አፍሪካውያን ነን” በማለት የሰጡትንም አስተያየት ሙሳ ፋኪ በመጥቀስ አስታውሰዋቸዋል።

A statue of Julius Nyerere, the Tanzanian freedom fighter, was erected in Addis Ababa, the seat of the African Union.

Julius Nyerere was a fighter who played a major role in the liberation of Tanzania, or Tanganyika as it was formerly known, from British colonial oppression.

After his country gained independence, Nyerere led the Europeans from 1961-1985.

Known as Mwalimu (Teacher) in Swahili, Nyerere is credited with his commitment to the ideals of Pan-Africanism.

They also gave refuge in Tanzania to freedom fighters who were fighting against the oppressive white rule, or apartheid, in South Africa.

He is one of the leaders who played a key role in the establishment of the Organization of African Unity.

African Union Commission Chairman Musa Faki Mahamat inaugurated the statue in a ceremony attended by many African leaders and praised them for their contribution to the continent.

When the Organization of African Unity was founded in Europe in 1963, Nyerere said, “Our continent is one.” We are all Africans,” Musa Faki reminded them.

Design a site like this with WordPress.com
Get started