በዚህም ሳቢያ የሕዝቡ መደበኛ እንቅስቃሴዎች የተስተጓጎሉ ሲሆን፣ የመንግሥታዊ መሥሪያ ቤቶች፣ የትራንስፖርት፣ የንግድ፣ የትምህርት እና የጤና አገልግሎቶች በጉልህ በሚታይ ሁኔታ መደናቀፍ እንደገጠማቸው ነዋሪዎች ይናገራሉ።
የሕይወት እና የሞት ጉዳይ የሆነው የጤና አገልግሎት የማግኘት ጉዳይ በተለያዩ የክልሉ አካባቢዎች የሚኖሩ ሰዎችን የሚያሳስብ ጉዳይ ሆኗል።
ከእነዚህም መካከል መደበኛ ክትትል እና ህክምና የሚያስፈልጋቸው እናቶች እና ህጻናት እንዲሁም የተለያዩ ዘላቂ የጤና ችግር ያለባቸው ሰዎች በአሳሳቢ ሁኔታ ውስጥ እንደሚገኙ ይናገራሉ።
እየተካሄደ ባለው ግጭት ምክንያት በብዙ ቦታዎች ላይ አስፈላጊ የሆኑ የጤና አገልግሎቶችን ለማግኘት ህሙማን ወደ ጤና ተቋማት መሄድ አለመቻልን ጨምሮ የመድኃኒት እና ሌሎች የህክምና ግብዓት እጥረት እንዲሁም የጤና ተቋማት ሥራ ማቆም እየተስተዋለ ነው።
በተጨማሪም የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን ከሚያስፈጽሙ የዕዝ ማዕከላት አንዱ የሆነው የማዕከላዊ ሸዋ ኮማንድ ፖስት ከሳምንታት በፊት ከደብረ ብርሃን ወደ ደሴ የሚወስደው መንገድን ላልተወሰነ ጊዜ በመዝጋት ከእንቅስቃሴ ውጪ ማድረጉ ሌላ ጫናን መፍጠሩን ነዋሪዎች እና የጤና ባሙያዎች ይናገራሉ።
ከየካቲት 16/2016 ዓ.ም. ጀምሮ የተዘጋው የመንገድ ትራንስፖርት መስመር በደብረ ብርሃን – በሸዋ ሮቢት እና በደሴ መካከል ያለ 267 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን የፌደራል አውራ ጎዳና ነው። በዚህም ሳቢያ ነዋሪዎች የተለያዩ ችግሮች እንደገጠሟቸው ለቢቢሲ ገልጸዋል።
Since the middle of last year, the unrest in the Amhara region has worsened and led to a separate armed conflict. The conflict taking place in many areas of the region is putting heavy pressure on the daily life of the people.
As a result, the normal activities of the people have been disrupted and residents say that government offices, transport, business, education and health services have been significantly disrupted.
Access to health services, which is a matter of life and death, has become a concern of people living in different parts of the region.
Among them, mothers and children who need regular monitoring and treatment, as well as people with various chronic health problems, are in a critical situation.
As a result of the ongoing conflict, patients are not able to go to health facilities to get essential health services in many places, lack of medicine and other medical resources, and health facilities have stopped working.
In addition, residents and health officials say that one of the command centers enforcing the emergency declaration, the Central Showa Command Post, closed the road from Debre Berhan to Dese for an indefinite period of time and put it out of action.
From February 16/2016 The road transport route that has been closed since is a 267-kilometer federal highway between Debre Berhan – Showa Robit and Desa. As a result, residents have faced various problems, they told the BBC.


Leave a comment