ድንገተኛውን የሩሲያ ድብደባ ተከትሎ በመላ ዩክሬን የአገሪቱ ጦር በተጠንቀቅ ላይ ይገኛል።
የሩሲያ የአየር ድብደባ ከፖላንድ የምትዋሰነው ሊቪቭ ግዛትን መምታቱን ተከትሎ ፖላንድ የአየር ኃይሏ በተጠንቀቅ ላይ እንዲሆን አዛለች።
በመዲናዋ ኪዬቭ ላይ የአየር ድብደባው የጀመረው በአገሪቱ ሰዓት አቆጣጠር እሑድ ንጋት 11 ሰዓት አካባቢ ነው።
የዩክሬን ጦር አየር ኃይሉ የሩሲያን ጥቃት በመከላከል ተጠምዷል ብሏል።
የጦሩ ዋና አስተዳዳሪ ሴርሂይ ፖፕኮ በርካታ የሩሲያ ሚሳኤሎች በኪዬቭ እና በዙሪያዋ የሚገኙ ዒላማዎቻቸውን ከመምታታቸው በፊት ተመትተው ወድቀዋል ብለዋል።
ይህን የሩሲያ ጥቃት ተከትሎ እስካሁን ድረስ በዩክሬን ላይ የደረሰ ጉልህ የሆነ ጉዳት ወይም በሰላማዊ ሰዎች ላይ የደረሰ ሞት ስለመኖሩ ሪፖርት አልተደረገም።
የሊቪቭ ግዛት ዋና ከተማ የሆነችው የሊቪቭ ከተማ ከንቲባ አንድሪይ ሳዶቨይ መላ ግዛቱን ዒላማ ያደረጉ 20 ሚሳኤሎች እና በርካታ ሰው አልባ አውሮፕላኖች መተኮሳቸውን በቴሌግራም ገጻቸው አስታውቀዋል።
ከንቲባው ጥቃቶቹ እስካሁን ድረስ ከተማዋን ባይመቱም በግዛቱ የሚገኙ “ቁልፍ የሆኑ መሠረተ ልማቶችን” ዒላማ አድርገዋል ብለዋል።
Ukraine’s capital, Kiev, has been hit by sudden Russian airstrikes.
Following the sudden Russian strike, the country’s military is on high alert across Ukraine.
Poland has ordered its air force to be on high alert after Russian airstrikes hit the Polish province of Lviv.
The airstrikes on the capital city of Kiev began at around 11:00 a.m. local time on Sunday.
Ukraine’s military says its air force is busy fending off Russian aggression.
Defense chief Sergei Popko said several Russian missiles had been shot down before hitting their targets in and around Kiev.
There have been no reports of significant casualties or civilian deaths in Ukraine following this Russian attack.
Andrey Sadovey, the mayor of Lviv, the capital of Lviv region, announced on his Telegram page that 20 missiles and several drones were fired at the entire region.
The mayor said the attacks had not yet hit the city but targeted “key infrastructure” in the state.


Leave a comment