ከለንደን የሚተላለፈው የኢራን ቴሌቪዢን አቅራቢ ለንደን ከሚገኘው ቤቱ ውጪ በተደጋጋሚ በስለት መወጋቱን ጣቢያው አስታወቀ።
ከአንድ ዓመት በፊት በኢራን ውስጥ የተቀሰቀሰውን ፀረ መንግሥት ተቃውሞ በስፋት ሲዘግብ የነበረው ‘ኢራን ኢንተርናሽናል’ የተባለው ቴሌቪዢን አቅራቢ ፑሪያ ዜራቲ ጥቃቱ የተፈጸመበት በቡድን ነው ተብሏል።
የለንደን ፖሊስ የፀረ ሽብርተኝነት መኮንኖች ቡድን በቴሌቪዥን አቅራቢው ላይ የተፈጸመውን ጥቃት ምርመራ እየመራው መሆኑ ተገልጿል።
ጥቃቱ የተፈጸመበት ግለሰብ በአሁኑ ጊዜ ሆስፒታል ውስጥ በደህና ሁኔታ እንደሚገኝም ፖሊስ አስታውቋል።
ምርመራ እያደረገ ያለው ፖሊስ እንዳለው፣ የጥቃቱ ሰለባ የሆነው ግለሰብ በዩናይትድ ኪንግደም ውስጥ በሚገኝ የፋርስ ቋንቋ የመገናኛ ብዙኃን ጋዜጠኛ መሆኑን ገልጿል።
በተጨማሪም ከዚህ በፊት በጣቢያው ላይ ይሰነዘሩ በነበሩ ማስፈራሪያዎች ምክንያት ለጉዳዩ ትኩረት ሰጥቶ እየተከታተለ ሲሆን፣ ለቅድመ ጥንቃቄም አስፈላጊውን ጥበቃ እንደሚደረግ ፖሊስ አስታውቋል።
ከጥቃቱ ጋር በተገናኘ አስካሁን በቁጥጥር ስር የዋለ ሰው የለም።
The station announced that an Iranian television presenter who broadcasts from London was repeatedly stabbed outside his home in London.
Puriya Zerati, the television presenter of Iran International, who was covering the anti-government protests in Iran a year ago, was allegedly attacked by a group.
A team of London police counter-terrorism officers is leading the investigation into the attack on the TV presenter, it has been reported.
Police also announced that the person who was attacked is currently in a safe condition in the hospital.
According to police who are investigating, the victim of the attack is a journalist with a Persian-language media outlet in the United Kingdom.
In addition, due to the threats that were made on the station in the past, the police are paying attention to the matter and the necessary security will be provided as a precaution.
No one has yet been arrested in connection with the attack.


Leave a comment