በእያንዳንዱ መኪና ላይ ያነጣጠረ ጥቃት ተፈጽሞም ሰባት ሰራተኞቻቸው እንደተገደሉም የድርጅቱ ኃላፊ ሆዜ አንድሬስ ገልጸዋል።
ሰኞ ዕለት የተፈጸመው ጥቃት በስህተት እንዳልሆነ የሚናገሩት ኃላፊው፣ ስለ ሰራተኞቻቸው አጠቃላይ እንቅስቃሴ ለእስራኤል ኃይል ቀድመው ማሳወቃቸውንም በድጋሚ ተናግረዋል።
እስራኤል የረድዔት ሰራተኞቹ ተሳፍረው ይሄዱበት በነበሩ መኪኖች ላይ በፈጸመችው ጥቃት አውስትራሊያዊ፣ ካናዳዊ፣ የዩናይትድ ኪንግደም፣ አሜሪካዊ እና ፍልስጤማዊ ዜግነት ያላቸው ሰራተኞች ተገድለዋል።
እስራኤል ጥቃቱ “ትልቅ ስህተት ነው” ስትል ይቅርታ የጠየቀች ሲሆን ገለልተኛ ምርመራ ለማድረግም ቃል ገብታለች።
እንደ ረድዔት ተቋሙ ገለጻ የእርዳታ መኪኖቹ ጥቃት የተፈጸመባቸው ዴይር አል ባላህ ከተሰኘው የእርዳታ ማከማቻ በባህር በኩል ለጋዛ የሚሆን ከ100 ቶን በላይ ምግብ አውርደው ሲወጡ ነው።
ጥቃት የተፈጸመባቸው ሦስቱ የእርዳታ መኪኖች የረድዔት ድርጅቱን አርማ በግልጽ የሚያሳዩ ነበሩ።
የወርልድ ሴንትራል ኪችን መስራች ዝነኛው ሼፍ ሆዜ “መጥፎ ዕድል፣ ውይ ቦምቡን በተሳሳተ ቦታ ጣልነው፣ የሚባል አይደለም” ሲሉም ለሮይተርስ የዜና ወኪል ተናግረዋል።
The head of the aid organization World Central Kitchen, whose workers were killed in Gaza, said Israeli forces “attacked their vehicles in a planned manner.”
Jose Andres, the head of the company, said that an attack was carried out targeting each car and seven of its employees were killed.
The official, who insisted that Monday’s attack was not accidental, reiterated that they had informed the Israeli forces in advance of the general movement of their personnel.
Australian, Canadian, UK, American and Palestinian workers have been killed in Israeli attacks on aid workers’ vehicles.
Israel apologized for the attack, saying it was a “big mistake” and promised an independent investigation.
According to the aid agency, the aid trucks were attacked when they were leaving Deir al-Balah aid depot by sea to unload more than 100 tons of food for Gaza.
The three aid trucks that were attacked were clearly displaying the logo of the aid organization.
“It’s bad luck, we dropped the bomb in the wrong place, it’s not,” celebrity chef Jose, founder of World Central Kitchen, told Reuters news agency.


Leave a comment