በጋዛ ናስር እና አል-ሺፋ ሆስፒታሎች ላይ የደረሰው ውድመት እና ከእስራኤል ወረራ በኋላ በሆስፒታሎቹ “የጅምላ መቃብሮች” መገኘታቸው “አሰቃቂ” ነው ሲሉ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሰብዓዊ መብት ኃላፊ ገለጹ።

ቮልከር ቱርክ በሟቾች ዙሪያ ገለልተኛ ምርመራ እንዲደረግም ጠይቋል።

የፍልስጤም ባለስልጣናት በናስር ሆስፒታል በጅምላ የተቀበሩ ወደ 300 የሚጠጉ ሰዎችን አስከሬን ማውጣታቸውን ተናግረዋል። ሰዎቹ እንዴት እንደሞቱ እና መቼ እንደተቀበሩ ግን ግልጽ አይደለም።

የእስራኤል ጦር አስከሬኖቹን ቀብሯል መባሉን “መሰረተ ቢስ” ሲል አጣጥሎታል።

ጦሩ በዃን ዮኒስ ከተማ በሚገኘው ሆስፒታል ለሁለት ሳምንታት በቆየ ዘመቻ ወቅት ታጋቾች ሊኖሩ እንደሚችሉ በመጠርጠሩ በፍልስጤማውያን የተቀበሩ አስከሬኖችን “መመርመሩን” አስታውቋል።

ከእገታ ነጻ የወጡ 10 ታጋቾች በናስር ሆስፒታል ለረጅም ጊዜ ተይዘው መቆየታቸውን ተናግረዋል።

የእስራኤል ጦር በናስር ካደረገው ዘመቻ በፊት በአካባቢው በነበረው ጦርነት ምክንያት ወደ መቃብር ስፍራዎች መሄድ ባለመቻላቸው በሆስፒታሉ ቅጥር ግቢ ውስጥ አስከሬን ለመቅበር ተገድደው እንደነበረ የሆስፒታሉ ባልደረቦች ገልጸው ነበር።

የእስራኤል ጦር በጋዛ የሚገኙ በርካታ ሆስፒታሎች ወረራ የፈጸመው የሐማስ ተዋጊዎች ስለሚንቀሳቀሱባቸው ነው ቢልም ታጣቂ ቡድኑ እና የህክምና ባለስልጣናት ይህን ያስተባብላሉ።

ጦርነቱ የተጀመረው የሐማስ ታጣቂዎች መስከረም 26 በደቡባዊ እስራኤል ድንበር ተሻግረው በፈጸሙት ጥቃት አንድ ሺህ 200 የሚጠጉ ሰዎችን ከገደሉ እና 253 ሰዎችን አግተው ወደ ጋዛ ከወሰዱ በኋላ ነበር።

ጦርነቱን ተከትሎ አብዛኞቹ ህጻናት እና ሴቶች የሆኑ ከ34 ሺህ 180 በላይ ሰዎች በጋዛ መገደላቸውን በሐማስ የሚመራው የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ገልጿል።

The destruction of Gaza’s Nasr and Al-Shifa hospitals and the discovery of “mass graves” at the hospitals after the Israeli occupation are “horrific”, the UN human rights chief said.

Volker also called on Turkey to conduct an independent investigation into the deaths.

Palestinian authorities say they have exhumed the bodies of nearly 300 people who were buried in a mass burial at Nasser Hospital. It is unclear how the men died and when they were buried.

He dismissed claims that the Israeli army had buried the bodies as “baseless”.

The army announced that it had “investigated” bodies buried by Palestinians on suspicion of hostages during a two-week operation at a hospital in Yunis.

He said that 10 hostages who were freed were detained in Nasser Hospital for a long time.

Colleagues of the hospital stated that before the Israeli army’s operation in Nasser, they were forced to bury bodies in the hospital’s premises because they could not go to the cemeteries due to the war in the area.

The Israeli army has raided several hospitals in Gaza because Hamas fighters are operating in them, but the militant group and medical officials deny this.

The war began after Hamas militants crossed the southern Israeli border on September 26, killing about 1,200 people and abducting 253 people to Gaza.

Following the war, more than 34,180 people, mostly children and women, have been killed in Gaza, according to the Hamas-led Ministry of Health.

Design a site like this with WordPress.com
Get started