በሐሰተኛ ሰነድ ከአፍሪካ ኅብረት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አካውንት ገንዘብ ለማውጣት በመሞከር የተጠረጠሩት ቀሲስ በላይ መኮንን እና ሌሎች ሁለት ተጠርጣሪዎች ላይ የክስ መመሥረቻ 15 ቀናት በፍርድ ቤት መፈቀዱን ጠበቃ አቶ ቱሊ ባይሳ ለቢቢሲ ተናገሩ።

የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ጊዜ ቀጠሮ ችሎት ይህንን ውሳኔ ያስተላለፈው ዛሬ ሐሙስ 24/ 2016 ዓ. ም. ረፋድ ላይ በነበረው የፍርድ ቤት ውሎው ነው።

ቀሲስ በላይ እንዲሁም አብረው በቁጥጥር ሥር የዋሉት አጃቢያቸው እና ሹፌራቸው ዛሬ ለሦስተኛ ጊዜ ፍርድ ቤት የቀረቡት፤ ባለፈው ሳምንት በነበረው ችሎት ፍርድ ቤቱ ለመርማሪ ፖሊስ ስምንት ተጨማሪ የምርመራ ቀናት በመፍቀዱ ነው።

እነ ቀሲስ በላይ የተጠረጠሩት በአፍሪካ ኅብረት ስም የተዘጋጀ ሐሰተኛ ሰነድ በመጠቀም በኅብረቱ ዋና መሥሪያ ቤት ቅጥር ግቢ ከሚገኘው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቅርጫፍ ስድስት ሚሊዮን 50 ሺህ ዶላር ለማውጣት ሞክረዋል በሚል ነው።

ባለፈው ሳምንት በነበረው ችሎት መርማሪ ፖሊስ ተጨማሪ ቀናት የተፈቀደለት ቀሲስ በላይ ቤት ውስጥ ባደረገው ብርበራ ያገኘው ሽጉጥ ፈቃድ ያለው ስለመሆኑ ለማጣራት፣ ሌሎች ስድስት ተጠርጣሪዎችን ለመያዝ እንዲሁም ለባንክ እና “ለተለያዩ የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች” ላቀረበው ጥያቄ ምላሽ ለመጠበቅ በሚል ነበር።

በዛሬው ችሎት ላይ መርማሪ ፖሊስ የሚያደርገውን ምርመራ እንዳጠናቀቀ ለፍርድ ቤቱ መግለጹን የቀሲስ በላይ ጠበቃ አቶ ቱሊ ተናግረዋል።

Lawyer Ato Tuli Baisa told BBC that 15 days of prosecution was granted against the priest Balai Mekonon and two other suspects who are suspected of trying to withdraw money from the account of the African Union Commercial Bank of Ethiopia with forged documents.

The Arada Division of the Federal Court of First Instance passed this decision today, Thursday 24/2016. m. It was at his court appearance in the early hours of the morning.

Kasis Bai, along with his accomplice and driver who were arrested together, appeared in court for the third time today; In last week’s hearing, the court granted eight more days of investigation to the investigating police.

The priests are suspected of having tried to withdraw six million and 50 thousand dollars from the branch of the Commercial Bank of Ethiopia located in the compound of the headquarters of the African Union using a fake document prepared in the name of the African Union.

In last week’s hearing, the investigating police were granted extra days to investigate whether the gun found in a search of the priest’s house was licensed, to arrest six other suspects and to wait for the bank and “various government offices” to respond to the request.

At today’s hearing, the lawyer of Kesis Bai, Ato Tuli, said that he told the court that the investigating police had completed the investigation.

Design a site like this with WordPress.com
Get started