በከፍተኛ ጎርፍ እና የመሬት መንሸራተት ሳቢያ ሰዎች መሞታቸው ተገለጸ።

በአገሪቱ ደቡባዊ ክፍል 56 ሰዎች እንደሞቱ የተገለጸ ሲሆን፣ በሪዮ ግራንድ ደ ሱል 67 ሰዎች የደረሱበት እንዳልታወቀ ተገልጿል።

ወደ 25,000 ሰዎች ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለዋል።

ግማሽ ሚሊዮን የሚጠጉ ሰዎች የኤሌክትሪክ አገልግሎት እና የንጹህ ውሃ አቅርቦት ተቋርጦባቸዋል።

በቀጣይም ከፍተኛ ዝናብ ይጠበቃል።

ይህ የአየር ንብረት ለውጥ የተከሰተው ከመደበኛው ጊዜ የከፋ ሙቀት፣ ወበቅ እና ንፋስ በመከሰቱ ነው።

ከአጠቃላይ 497 ከተሞች ግማሹ አውሎ ንፋስ ገጥሟቸዋል። አውራ ጎዳናዎችና ድልድዮች ላይም ጉዳት ደርሷል።

የመሬት መንሸራተቱ ከውሃ ኃይል የሚያመነጭ ግድብ ላይ ጉዳት አድርሷል። ቤንቶ ጎንካልቭስ በተባለ ከተማ 30 ሰዎች ሞተዋል።

በውሃ መሙላት ምክንያት ሌላ ግድብም ይፈርሳል ተብሎ ተሰግቷል።

በፖርቶ አልግሬ ከመጠን በላይ በሞላ ወንዝ ምክንያት፣ መንገዶች በጎርፍ ተጥለቅልቀዋል። መንደሮችም ከውሃ ሥር ሰጥመዋል።

Deaths were reported due to heavy floods and landslides.

In the southern part of the country, 56 people have been reported dead, and in Rio Grande de Sul, 67 people have been reported unaccounted for.

About 25,000 people have been displaced from their homes.

About half a million people are without electricity and clean water.

Heavy rain is also expected.

This climate change is caused by warmer than normal temperatures, droughts and winds.

Half of the total of 497 cities were hit by hurricanes. Highways and bridges were also damaged.

The landslide damaged a hydroelectric dam. 30 people died in a town called Bento Goncalves.

Another dam is also feared to collapse due to water filling.

Due to an overflowing river in Porto Alegre, roads are flooded. Villages were submerged under water.

Design a site like this with WordPress.com
Get started