በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ዳውሮ ዞን፤ ሶስት ሬክተር ስኬል ሆኖ የተመዘገበ የመሬት መንቀጥቀጥ መከሰቱን የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የጂኦፊዚክስ፣ ህዋ ሳይንስ እና አስትሮኖሚ ኢንስቲትዩት አስታወቀ።

የመሬት መንቀጥቀጡ በዞኑ በሚገኙ አስሩም ወረዳዎች እና ሁለት የከተማ መስተዳድሮች እንደተከሰተ የዳውሮ ዞን የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ፅህፈት ቤት ገልጿል።

በዳውሮ ዞን የመሬት መንቀጥቀጡ የተመዘገበው ዛሬ ማክሰኞ ሚያዝያ 29፤ 2016 ዓ.ም. ከጠዋቱ አንድ ሰዓት ከ24 ደቂቃ መሆኑን በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የሶሲሞሎጂ ትምህርት ክፍል ኃላፊ ፕሮፌሰር አታላይ አየለ ለቢቢሲ ተናግረዋል። የሶሲሞሎጂ ትምህርት ክፍል ኃላፊው እንደሚያስረዱት፤ ተቋሙ ከዚህ ቀደም ባለው ልምድ የመሬት መንቀጥቀጥን የተከሰተበትን ቦታ በትክክል ለማግኘት ከሶስት በላይ ጣቢያዎች የተመዘገቡ መረጃዎችን ይጠቀማል።

በዛሬው ዕለት ግን በኢንተርኔት መቋረጥ ምክንያት መረጃ ማግኘት የተቻለው አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ውስጥ ከሚገኝ ጣቢያ ብቻ መሆኑን የጠቀሱት ፕሮፌሰር አታላይ፤ የመሬት መንቀጥቀጡ የተከሰተው “በዳውሮ አካባቢ ነው” ብሎ መውሰድ እንደሚቻል ተናግረዋል።

ኢንስቲትዩቱ፤ አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ውስጥ በሚገኝ ጣቢያው የመዘገበው የመሬት መንቀጥቀጥ “በሬክተር ስኬል ወደ ሶስት የሚገመት” መሆኑን ፕሮፌሰል አታላይ ገልጸዋል።

ቢቢሲ ያነጋገራቸው ሁለት የዳውሮ ዞን የታርጫ ከተማ ነዋሪዎች ጠዋት አንድ ሰዓት ተኩል ገደማ ላይ ለሰከንዶች የቆየ የመሬት መንቀጥቀጥ እንደተሰማቸው ተናግረዋል። አቤኔዘር ተስፋዬ የተባለ የታርጫ ከተማ ብርሃን መንደር ነዋሪ፤ “መሬት ላይ ተኝቼ ነበር፣ [መሬቱ] እንደተንቀሳቀሰ ተሰምቶኛል። ከዚያ ባለፈ ድምፅም ነበር” ሲል የነበረውን ሁኔታ አስረድቷል።

Dauro Zone in Southwest Ethiopia Region; Addis Ababa University’s Institute of Geophysics, Space Science and Astronomy announced that an earthquake of magnitude 3 occurred.

Dauro Zone Government Communication Office stated that the earthquake occurred in all ten districts and two city governments in the zone.

The earthquake in Dauro zone was recorded today, Tuesday, April 29; 2016 Professor Atalai Ayele, Head of the Department of Sociology at Addis Ababa University, told the BBC that it was one hour and 24 minutes in the morning. As the head of Sociology Department explains; The institute uses data from more than three stations to pinpoint the exact location of earthquakes based on past experience.

Prof. Atalai mentioned that today, due to the interruption of the Internet, it was only possible to get information from a site in Addis Ababa University. He said that it can be assumed that the earthquake occurred “in the area of ​​Dauro”.

The Institute; Prof. Atalai stated that the earthquake recorded by the station located in Addis Ababa University was “approximately three on the Richter scale”.

Two residents of the town of Tarcha in the Dauro zone who spoke to the BBC said that they felt an earthquake that lasted for seconds at about 1:30 in the morning. Ebenezer Tesfaye, a resident of Berhan Village in Tarcha City; “I was lying on the ground, I felt [the ground] move. Beyond that, there was a voice,” he explained.

Design a site like this with WordPress.com
Get started