ለተቃውሞ የወጡ እስራኤላውያን ወደ ጋዛ የሚሄዱ የእርዳታ መኪኖችን በማገድ የተጫኑ ምግቦችን አውርደው መንድ ላይ በመወርወር እና የእህል ከረጢቶችን ቀደው በተኑ።

እስራኤላውያኑ ይህንን የፈጸሙት በትናትናው ዕለት እስራኤል በኃይል ተቆጣጥራት በምትገኘው ዌስት ባንክ ነው።

ከዮርዳኖስ የመጡት እርዳታ የጫኑት መኪኖች ከኬብሮን በስተምዕራብ ታርኩሚያ የፍተሻ ጣቢያ እያቀኑ ነበር ተብሏል።

እርዳታው በከፍተኛ የምግብ እጥረት እና ጠኔ ለተመቱ ፍልስጤማውያን የሚውል ነበር።

ዋይት ሃውስ ይህንን ጥቃት አውግዞ የእርዳታ ጭነቶቹን መዘረፍ “አሳፋሪ ስራ” ሲል ገልጾታል።

ከተቃውሞው ጀርባ ያለው ቡድን እስራኤላውያን ታጋቾች በጋዛ አለመለቀቃቸውን ለመቃወም የተደረገ ነው ማለቱ ተዘግቧል።

በተቃውሞ ሰልፉ የነበሩ ግለሰቦች የእርዳታ መኪኖቹ የጫኗቸውን ሳጥኖች መሬት ላይ ሲጥሉ እና በእግራቸው ሲረግጧቸው የሚያሳዪ ያልተረጋገጡ ቪዲዮዎች በማህበራዊ ሚዲያ ድረገጾች ተሰራጭተዋል።

አንዳንድ ቪዲዮዎች ደግሞ ተሽካርካሪዎችን ሲያቃጥሏቸው የሚያሳዩ ሲሆን ቢቢሲ የእነዚህን ቪዲዮዎች ትክክለኛነት ማረጋገጥ አልቻለም።

የእስራኤል መገናኛ ብዙኃን እንደዘገቡት ይህንን የተቃውሞ ሰልፍ ያዘጋጀቸው ትዛቭ 9 የተሰኘ ቡድን ነው።

Protesting Israelis blocked aid trucks heading to Gaza, unloaded laden food, threw it onto trees, and tore sacks of grain and scattered them.

The Israelis did this yesterday in the West Bank, which is controlled by Israel.

The aid trucks from Jordan were said to be heading to the Tarkumiya checkpoint west of Hebron.

The aid was intended for the Palestinians who were suffering from severe food shortages and famine.

The White House condemned the attack, calling the looting of aid shipments a “disgraceful act.”

The group behind the protest reportedly said it was to protest the non-release of Israeli hostages in Gaza.

Unverified videos have been circulated on social media showing protesters throwing boxes loaded with aid trucks on the ground and trampling them with their feet.

Some videos also show vehicles being set on fire, and the BBC has not been able to confirm the authenticity of these videos.

According to Israeli media reports, this protest was organized by a group called Tzav 9.

Design a site like this with WordPress.com
Get started