የጦር መሣሪያ እጥረት ያጋጠማቸው የዩክሬን ወታደሮች እየገሰገሱ እየመጡ ያሉ የሩሲያ ወታደሮችን መቋቋም አቅቷቸዋል።
ዜሌንስኪ፤ የጦር ሠራዊት ሞራል እና ቁሳቁስ እንዳጠረው አምነው በርካታ ብርጌዶች አሁን ባዶ ሆነዋል ብለዋል።
ኤኤፍፒ ለተሰኘው የዜና ወኪል ድምፃቸውን የሰጡት ፕሬዝደንቱ የሀገሪቱ አየር ኃይል እንደተመናመነ አሳውቀው አጋር ሀገራት ተጨማሪ የአየር መከላከያ እና ተዋጊ ጄቶች እንዲልኩ ተማፅነዋል።
“ዩክሬንን ለመከላከል ከሚያስፈልገን አቅም አሁን ያለን 25 በመቶው ብቻ ነው” ሲሉ ስለአየር ኃይሉ ተናግረዋል።
“ሩሲያ በአየር ኃይል እንዳትበልጠን ቢያንስ 120 አሊያም 130 ዘመናዊ ጄቶች ያስፈልጉናል” ብለዋል።
ዩናይትድ ስቴትስ በቅርቡ የጦር መሣሪያ እርዳታን ጨምሮ 61 ቢሊዮን ዶላር ድጋፍ ለዩክሬን ማድረጓ ይታወሳል።
የሩሲያ ኃይሎች በቅርቡ የበጋ ወራት ጥቃት የጀመሩ ሲሆን በዩክሬን ሰሜን ምስራቅ አቅጣጫ የሚገኙ በርካታ ሥፍራዎችን በቁጥጥራቸው ሥር እያዋሉ ነው።
Ukrainian President Volodymyr Zelenskiy warned that Russia may intensify its attacks in the northeastern part of the country following its recent control of the city of Kharkiv.
Ukraine’s underarmed troops are unable to withstand advancing Russian troops.
Zelensky. He admitted that the army’s morale and material had decreased and many brigades were now empty.
The president, who gave his voice to the news agency AFP, announced that the country’s air force has been depleted and appealed to allied countries to send more air defense and fighter jets.
“We currently have only 25 percent of the capabilities we need to defend Ukraine,” he said of the air force.
“We need at least 120 or 130 modern jets so that Russia does not surpass us in air power,” he said.
The United States has recently provided $61 billion in military aid to Ukraine.
Russian forces have recently launched an offensive over the summer and are taking control of several areas in northeastern Ukraine.


Leave a comment