ኬንያ ውስጥ ጫት መቃም እየጨመረ ላለው የአእምሮ ጤና ችግር፣ ለወንጀልን መስፋፋት እንዲሁም ለተለያዩ ማኅበራዊ ችግሮች ምክንያት ነው ተብሎ ይታሰባል።
በኬንያ የባሕር ዳርቻ አካባቢ የሚገኙ ሦስት ግዛቶች ባለፈው ሳምንት ጫት መሸጥ እና መቃምን ካገዱ በኋላ ጫት በሚያምርቱ አካባቢዎች ቁጣን ቀስቅሷል።
የአገሪቱ ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ ግን ጫት ሕጋዊ ምርት መሆኑን ጠቅሰው ሽያጩም መከልከል የለበትም በማለት የግዛቶቹን እርምጃ ተቃውመዋል።
ሙጉካ በመባል የሚታወቀው የጫት ዓይነት ርካሽ እና ጠንካራነቱ የሚነገርለት ሲሆን ሞምባሳ፣ ኪሊፊ፣ ታይታ ታቬታ እና ክዋሌ በተባሉት የባሕር ዳርቻ ግዛቶች ውስጥ በስፋት ጥቅም ላይ ይውላል።
ባለፈው ሳምንት የሞምባሳ ግዛት አስተዳዳሪ አብዱልሰዋማድ ሸሪፍ ናሲር ሙጉኮ የተባለው የጫት ዓይነት በተለይ በወጣቶች ላይ ባለው ጎጂ ውጤት ምክንያት ወደ ግዛታቸው እንዳይገባ፣ እንዳይዘዋወር፣ አዳይሸጥ እና እንዳይቃም ከልክለዋል።
አስተዳዳሪው እንዳሉት ሞምባሳ ውስጥ በሚገኙ የሱስ መገገሚያ ማዕከላት ከሚታከሙት ከግማሽ በላይ የሚሆኑት የጫት ሱሰኞች ናቸው።
Kenyan President William Ruto has announced that some states in the country will reject the controversial ban on the sale of khat and allow the production to expand.
In Kenya, khat use is believed to be the cause of increasing mental health problems, rampant crime, and various other social problems.
Three states along Kenya’s coast last week banned the sale and cultivation of khat, sparking outrage in khat-growing areas.
The country’s President William Ruto, however, said that khat is a legal product and its sale should not be banned and he opposed the actions of the states.
A type of chaat known as muguka is said to be cheaper and stronger and is widely used in the coastal states of Mombasa, Kilifi, Taita Taveta and Kwale.
Last week, Mombasa State Governor Abdulsawamad Sheriff Nasir Muguko banned the importation, circulation, sale and cultivation of khat in his state due to its harmful effects especially on the youth.
According to the administrator, more than half of those treated at addiction rehabilitation centers in Mombasa are khat addicts.


Leave a comment