እስራኤል በሰው አልባ አውሮፕላን (ድሮን) በፈጸመችው ጥቃት ሰባት ሰራተኞቹ የተገደሉበት የረድዔት ድርጅት ጉዳዩ በገለልተኛ አካል እንዲጣራ ጠየቀ።

የእስራኤል መከላከያ ኃይል በተፈጸሙ “ከባድ ስህተቶች” የረድዔት ድርጅቱ ወርልድ ሴንትራል ኪችን ሰራተኞች ዒላማ ተደርገው ለሞት ተዳርገዋል ብሏል።

የእስራኤል ጦር ባደረገው ምርመራ ሁለት ከፍተኛ መኮንኖችን አባሯል።

የረድዔት ተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ በበኩላቸው የእስራኤል ጦር “በጋዛ ውስጥ የራሱን ውድቀት በታማኝነት መመርመር አይችልም” ብለዋል።

ሥራ አስፈጻሚዋ ኤሪን ጎሬ “የእስራኤል መከላከያ ኃይል በባልደረቦቻችን ላይ በተፈጸመው አሰቃቂ ግድያ ይቅርታ መጠየቃቸው ደካማ ማጽናኛ ነው። ለተጎጂ ቤተሰቦችም ሆነ ለወርልድ ሴንትራል ኪችን ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ በቂ አይደለም” ብለዋል።

የረድዔት ሰራተኞቹን ግድያ ተከትሎ በርካታ ተቋማት ሥራቸውን ያቆሙ ሲሆን እስራኤል በጋዛ ሰርጥ ውስጥ የሚንቀሳቀሱ የእርዳታ ሰራተኞችን ደኅንነት ለማረጋገጥ “ተጨባጭ እርምጃዎችን” ልትወስድ ይገባል ሲሉ ሥራ አስፈጻሚዋ ተናግረዋል።

እስራኤል አከናወንኩት ያለችውን እና ለሕዝብ ይፋ ያላደረገችውን የምርመራ ሙሉ ግኝትም እንድታትም ቁልፍ በሆኑ ምዕራባውያን አጋሮቿ ጫና እየተደረገባት ይገኛል።

An aid organization whose seven workers were killed in an Israeli drone attack has asked for an independent investigation into the matter.

Aid organization World Central Kitchen workers were targeted and killed due to “serious mistakes” by the Israel Defense Forces.

The Israeli army fired two senior officers following an investigation.

The chief executive of the aid agency said the Israeli army “cannot honestly investigate its own failure in Gaza”.

Executive director Erin Gore said: “The fact that the Israel Defense Forces have apologized for the brutal killing of our colleagues is of poor consolation. “It is not enough for the victims’ families and the international community for World Central Kitchen.”

Following the killing of the aid workers, several institutions have stopped working, and Israel must take “concrete steps” to ensure the safety of aid workers operating in the Gaza Strip, the executive said.

Israel is under pressure from its key Western allies to publish the full findings of an investigation it says it has carried out and which it has not made public.

Design a site like this with WordPress.com
Get started