ከአንድ ወር በላይ ተዘግቶ የቆየው የደብር ብርሃን – ደሴ መንገድ ከዛሬ መጋቢት 28/ 2016 ዓ.ም. ጀምሮ እንደሚከፈት የዞኑ ኮሙኒኬሽን ገለጸ።

መሥሪያ ቤቱ የማዕከላዊ ሸዋ ኮማንድ ፖስትን ጠቅሶ በማኅበራዊ ገጹ ላይ ባጋራው ጽሑፍ ከጸጥታ ችግር ጋር በተያያዘ ከየካቲት 16/2016 ዓ.ም አንስቶ ተቋርጦ የነበረው ከደብረ ብርሃን ደሴ የሚወስደው ዋና መንገድ ከዛሬ ጀምሮ ለመንገደኞች ክፍት እንደሚሆን አስታውቋል።

ኮማንድ ፖስቱ፣ መንገዱ እንዲከፈት የተወሰነው በአካባቢው ያለው የሰላም ሁኔታ በመሻሻሉ እና ኅብረሰተሰቡ ባቀረበው ጥያቄ መሠረት ነው ብሏል።

ከአዲስ አበባ በስተሰሜን ምሥራቅ 130 ኪሎሜትር ከምትርቀው የአማራ ክልል ፣ ሰሜን ሸዋ ዞን ዋና ከተማ ከሆነችው ደብረ ብርሃን ወደ ንግድ ከተማዋ ደሴ የሚወስደው መንገድ ላልተወሰነ ጊዜ ተዘግቶ እንዲቆይ የተወሰነው ኮማንድ ፖስቱ “ ፅንፈኛ” ያላቸው ኃይሎች ላይ እርምጃ እየወሰደ በመሆኑ ሰላማዊ ዜጎች ላይ ጉዳት እንዳይደርስ በሚል እንደሆነ ገልጾ ነበር።

“ፅንፈኛ” ሲል የገለጻቸው ኃይሎች እነማን እንደሆኑ ግን በስም አልጠቀሰም።

ሆኖም በአካባቢው የፋኖ ታጣቂዎች እንዲሁም መንግሥት ‘ኦነግ ሸኔ’ ሲል በሽብርተኝነት የፈረጀውና ራሱን የኦሮሞ ነጻናት ሰራዊት እያለ የሚጠራው ታጣቂ ቡድን እንደሚንቀሳቀሱ ይነገራል።

ከአዲስ አበባ ወደ ወደ የተለያዩ የአማራ ክልል ከተሞች የሚወስደው ይህ ዋና መንገድ ከዚህ ቀደም በተከሰቱ ጥቃቶች፣ ግጭቶች፣ እገታዎችና “ያለአግባብ” በጸጥታ ኃይሎች በሚደረጉ የኬላ ፍተሻዎች ምክንያት ሲዘጋና ሲከፈት ነበር።

Debar Berhan-Desi Road, which has been closed for more than a month, will be closed from today, March 28/2016. The zone communication said that it will be opened from now on.

The office quoted the Central Showa Command Post and announced in an article shared on its social media that the main road from Debre Berhan Dese, which had been closed since February 16/2016 due to security issues, will be open to travelers from today.

The command post said that the decision to open the road was based on the improvement of the peace situation in the area and the community’s request.

The road leading from Debre Berhan, the capital of North Showa Zone, Amhara Region, 130 kilometers northeast of Addis Ababa, to the commercial city of Dese has been closed for an indefinite period.

He did not name the forces he described as “extremist”.

However, it is said that Fano militants and a militant group that the government has labeled as terrorism and calling itself the Oromo Liberation Army are operating in the area.

This main road that leads from Addis Ababa to various cities in the Amhara region has been closed and reopened due to previous attacks, clashes, blockades and “unreasonable” checkpoints conducted by security forces.

Design a site like this with WordPress.com
Get started