በርካታ ኢትዮጵያውያን ስደተኞችን ይዛ ከጂቡቲ ወደ የመን በማቅናት ላይ የነበረች ጀልባ ኤደን ባሕረ ሰላጤ ውስጥ ሰጥማ የ38 ሕይወት አለፈ።

አደጋው የደረሰው ትናንት ሰኞ መጋቢት 30/2016 ዓ.ም. ኢትዮጵያውያኑን አሳፍራ ከጅቡቲ ወደ የመን ስትጓዝ ነው ጀልባዋ የመስመጥ አደጋ ያጋጠማት።

በጅቡቲ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ በሰሜን ምሥራቅ ከሚገኘው የአገሪቱ ክፍል ተነስታ ጉዞዋን ወደ የመን አቅጣጫ አድርጋ የነበረችው ጅልባ 60 ኢትዮጵያውያንን አሳፍራ ነበር ብሏል።

የተባበሩት መንግሥታት የስደተኞች ድርጅት በአደጋው ሕይወታቸው ያለፉ ሰዎችን ዜግነትን በተመለከተ ያለው ነገር ባይኖርም፤ ከሟቾቹ መካከል ሕጻናት እንደሚገኙበት ገልጾ 22 ሰዎች በሕይወት ተገኝተዋል ብሏል።

የተባባሩት መንግሥታት የፍልሰተኞች ድርጅት (አይኦኤም) በጀልባዋን ላይ ተሳፍረው የነበሩ ሰዎችን ቁጥር 64 የሚያደርሰው ሲሆን፣ ሕይወታቸው ሳያልፍ አይቀርም የተባሉ ተጨማሪ 6 ሰዎች የገቡበት አልታወቀም ብሏል።

በጅቡቲ የኢትዮጵያ ኤምባሲ አደጋው ወደ ደረሰበት ስፍራ በመጓዝ የአደጋውን መንስኤ በማጣራት ላይ እንደሚገኝም ጨምሮ ገልጿል።

A boat carrying many Ethiopian refugees from Djibouti to Yemen sank in the Gulf of Aden, killing 38 people.

The accident happened yesterday, Monday, March 30/2016. Asafra was traveling from Djibouti to Yemen when the boat sank.

The Ethiopian Embassy in Djibouti said that Jilba, which was traveling from the north-eastern part of the country to Yemen, was carrying 60 Ethiopians.

Although the United Nations Refugee Agency does not have anything regarding the citizenship of those who died in the disaster; He said that children were among the dead and 22 people were found alive.

The United Nations Organization for Migration (IOM) says that the number of people on board the boat is 64, and 6 more people who are believed to have died have not been identified.

The Ethiopian Embassy in Djibouti has traveled to the site of the accident and is investigating the cause of the accident, he said.

Design a site like this with WordPress.com
Get started