ይህ ኬንያ ያቀረበችው አማራጭ በቀጠናው የሚገኙ የባሕር በር የሌላቸው አገራት በንግድ ስምምነት መሠረት የባሕር መተላለፊያ አገልግሎት እና ጥቅም የሚያገኙበትን ዕድል የሚፈጥር ነው ተብሏል።
ከጥቂት ወራት በፊት ኢትዮጵያ እና ከሶማሊያ ተገንጥላ ነጻ አገርነቷን ካወጀችው ሶማሊላንድ ጋር የባሕር በር ለማግኘት የመግባቢያ ሠነደ መፈረሟ በአዲስ አበባ እና ሞቃዲሾ መካከል ከፍተኛ ውጥረትን ፈጥሯል።
ኢትዮጵያ እና ሶማሊላንድ ታኅሣሥ 22/2016 ዓ.ም. አዲስ አበባ ላይ በመሪዎቻቸው መካከል የተፈራረሙት የመግባቢያ ሠነድ ኢትዮጵያ ነጻ አገር መሆኗን ላወጀችው ሶማሊላንድ ዕውቅናን ለመስጠት፣ ሶማሊላንድ በምላሹ ለኢትዮጵያ የባሕር በር ለመፍቀድ ከስምምነት መድረሳቸው መዘገቡ ይታወሳል።
ይህንንም ሶማሊላንድን የግዛቱ አንድ አካል እንደሆነች የሚገልጸው የሶማሊያ መንግሥት ስምምነቱን አጥብቆ በመቃወም፣ የአገሪቱን ሉዓላዊነት የሚጥስ ድርጊት ነው በማለት አጥብቆ ተቃውሞታል።
ይህን ተከትሎ ሶማሊያ በሞቃዲሾ የሚገኘቱን የኢትዮጵያን አምባሳደር ከአገር አስወጥታ በአዲስ አበባ የሚገኙትን አምባሳደሯን ባለፈው ሳምንት ጠርታለች።
በሁለቱ የአፍሪካ ቀንድ አገራት መካከል የተፈጠረውን ውዝግብ ለማርገብ ኬንያ አሁን አማራጭ ያለችውን ሐሳብ ወደ ጠረጴዛ አምጥታለች።
Kenya offered an alternative to the Regional Coastal Service Agreement, which it said would ease tensions between Ethiopia and Somalia.
This option offered by Kenya is said to create opportunities for landlocked countries in the region to get access to sea passage services and benefits under trade agreements.
A few months ago, the signing of a memorandum of understanding with Ethiopia and Somaliland, which declared its independence from Somalia, to have access to a sea port, has created a lot of tension between Addis Ababa and Mogadishu.
Ethiopia and Somaliland December 22/2016 It will be remembered that the memorandum of understanding signed between their leaders in Addis Ababa to give recognition to Somaliland, which declared Ethiopia to be an independent country, Somaliland, in return, agreed to allow Ethiopia a sea gate.
The government of Somalia, which declares Somaliland as a part of its territory, strongly opposes the agreement, saying it violates the country’s sovereignty.
Following this, Somalia expelled the Ethiopian ambassador in Mogadishu and summoned its ambassador in Addis Ababa last week.
Kenya has now brought an alternative proposal to the table to ease the conflict between the two Horn of Africa countries.


Leave a comment