ታዳጊው ከዘጠኝ ቀናት በፊት መጋቢት 26፣ 2016 ዓ.ም. ከቀኑ 10፡00 ላይ ታፍኖ መወሰዱን ገልጸዋል።
አማን መሐመድ የተባለው ታዳጊ ከሚማርበት ዳባት አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ወደ ቤቱ በመመለስ ላይ ድንገት ፊታቸውን የሸፈኑ ሦስት ሰዎች የአማንን ፊት በመሸፈን በባጃጅ መውሰዳቸውን ወላጅ እናቱ ወይዘሮ ራሕማ መሐመድ ተናግረዋል።
ከትምህርት ቤት በሚመለስበት ወቅት መንገድ ላይ አግኝቶት የነበረው የ14 ዓመት ወንድሙ ግለሰቦቹ አፍነው ሲወስዱት ተመልክቷል ተብሏል።
ልጁ ታግቶ ከተወሰደ በኋላም በመቶ ሺህ ብሮች እንዲከፍሉ መጠየቃቸውን እናትየው ለቢቢሲ ገልጸዋል።
“800 ሺህ ብር ከከፈላችሁ ልጃችሁን በደቂቃዎች ውስጥ እናስረክባለን፤ ካልሆነ ግን በዶላር ይጨምራል” ሲሉ እያስፈራሩን ነው ብለዋል።
በዳባት በሚገኘው የኤርትራውያን የስደተኞች መጠለያ ካምፕ አለምዋጭ ውስጥ የሚኖሩት እናት አማርኛ ቋንቋ መናገር እንደማይችሉ እና “ልጄን አፍነው ወስደውታል ከሚሏቸው ግለሰቦች ጋር” በልጃቸው አማካይነት እየተነጋገሩ እንደሆነ ገልጸዋል።
His family told the BBC that a 12-year-old Eritrean refugee child was abducted by unknown individuals in Dabat District, Amhara Region, North Gondar Zone.
The teenager died nine days ago on March 26, 2016. They stated that he was abducted at 10:00 p.m.
His biological mother, Mrs. Rahma Muhammad, said that three masked men covered Aman’s face and took him away in a Bajaj while returning home from Dabat Primary School where Aman Muhammad was studying.
It is said that his 14-year-old brother, who met him on the road while returning from school, saw the men abducting him.
The mother told the BBC that after the child was taken hostage, they were asked to pay hundreds of thousands of Birr.
“If you pay 800 thousand birr, we will hand over your child in minutes; If not, it will increase in dollars,” he said, threatening us.
The mother who lives in Alemwach, an Eritrean refugee camp in Dabat, stated that she cannot speak Amharic and that she is communicating through her son with “persons who say they have kidnapped my son.”


Leave a comment