ታዋቂው አቡነ ማር ማሪ ኢማኑዔል ሲድኒ ከሚገኝ ቤተ-ክርስቲያን በቀጥታ ሥርጭት የሚተላለፍ ትምህርት እየሰጡ ሳለ ጥቃት ተፈፅሞባቸዋል።

አቡነ ማር ማሪ ኢማኑዔል የአሲሪያን ኦርቶዶክስ ክራይስት ዘ ጉድ ሼፐርድ የተባለው ቤተ-ክርስቲያን ወግ አጥባቂ መሪ ናቸው።

በአቡኑ ላይ ጥቃት ያደረሰው ታዳጊ በምዕመናን ቁጥጥር ሥር ከዋለ በኋላ ለፖሊስ ተላልፎ ተሰጥቷል።

የሲድኒ ፖሊስ አቡነ ማር ማሪ ኢማኑዔል እና አባ ኢሳክ የተበሉ ቄስ ጥቃት ቢደርስባቸውም “ሕይወታችን አደጋ ላይ የሚጥል አይደለም” ብሏል።

የ53 ዓመቱ አቡነ ማር ማሪ ኢማኑዔል ጭንቅላታቸው ላይ በስለት እንደተወጉ የተገለጠ ሲሆን፣ የኤንኤስደብሊው ፖሊስ ኮሚሽነር አቡኑ ቀዶ ህክምና እንደተደረገላቸው ገልጠው “በሕይወት በመትረፋቸው ዕድለኛ ናቸው” ብለዋል።

ግርማ ሞገስ ያላቸው እና አነጋጋሪ ስብከት በማሰማት የሚታወቁ ናቸው የሚባሉት አቡነ ማር ማሪ ኢማኑዔል በተለይ በአውሮፓ 2020 የኮቪድ-19 ሕግጋትን በመቃወም ነው ታዋቂነትን ያተረፉት።

ቤተ-ክርስቲያኗ አባ ማር ማሪ የሚያደርጉትን ትምህርት በማኅበራዊ ሚድያ አማካይነት በቀጥታ ታስተላልፋለች።

The famous Abune Mar Marie Emanuel was attacked while giving a live broadcast from a church in Sydney.

Abune Mar Marie Emmanuel is the conservative leader of the Assyrian Orthodox Church of Christ the Good Shepherd.

The teenager who attacked Abunu was handed over to the police after he was taken into custody by the congregation.

Sydney police said priests Abune Mar Marie Emmanuel and Father Issac were attacked but “our lives are not in danger”.

Abune Mar Marie Emmanuel, 53, was found stabbed in the head, NSW Police Commissioner Abunu said he underwent surgery and said he was “lucky to be alive”.

Abune Mar Marie Emanuel, who is said to be known for his majestic and eloquent sermons, gained fame especially for opposing the Covid-19 regulations in Europe 2020.

The church broadcasts Father Mar Marie’s teaching live through social media.

Design a site like this with WordPress.com
Get started