ዛሬ አርብ ጎህ ከመቅደዱ በፊት በማዕከላዊቷ የኢራን ከተማ ኢስፋሃን ፍንዳታዎች መሰማታቸውን የኢራን የመገናኛ ብዙኃን የዘገቡ ሲሆን፣ የአሜሪካ ባለሥልጣናትም ይህን አረጋግጠዋል።
እስራኤል በኢራን ላይ የሚሳኤል ጥቃት መፈጸሟን የዩናይትድ ስቴትስ ባለሥልጣናት በአሜሪካ የቢቢሲ አጋር ለሆነው ሲቢኤስ ቴሌቪዥን አረጋግጠዋል።
የኢራን መገናኛ ብዙኃን ደግሞ ሦስት የእስራኤል ድሮኖች በኢራን የአየር መከላከያ ሥርዓት መውደማቸውን ዘግበዋል።
ጥቃቱ ተፈጽሞባታል የተባለችው የኢራን ከተማ ኢስፋሃን የአገሪቱ አየር ኃይል መቀመጫ ስትሆን፣ በርካታ ወታደራዊም ተቋማት በውስጧ ይገኛሉ።
ጥቃቱ ከተፈጸመ ጥቂት ሰዓታት ብቻ ያለፉት በመሆናቸው አስካሁን ዒላማ ስለሆኑ ቦታዎች እና ስለደረሰ ጉዳት የወጣ መረጃ የለም። የኢራን መገናኛ ብዙኃንም የአገሪቱ የኑክሌር ተቋማት ላይ ምንም ጉዳት አለመድረሱን አመልክተዋል።
Iran’s media and US officials announced that Israel retaliated against Iran’s drone and missile attacks this morning.
Iranian media reported that explosions were heard in the central Iranian city of Isfahan before dawn on Friday, and US officials confirmed this.
US officials have confirmed to CBS Television, the US affiliate of the BBC, that Israel launched a missile attack on Iran.
Iranian media also reported that three Israeli drones were destroyed by Iran’s air defense system.
The Iranian city of Isfahan, where the attack is said to have taken place, is the seat of the country’s air force, and many military facilities are located in it.
Only a few hours have passed since the attack, so far there is no information about the target areas and casualties. Iran’s media also indicated that there was no damage to the country’s nuclear facilities.


Leave a comment