አርቲስት አማኑኤል ሀብታሙ፣ የቴአትር አዘጋጅ ዳግማዊ ፈይሳ እና በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ ታዋቂ የሆነችው ፍላጎት አብርሃምን ጨምሮ 20 ግለሰቦች “ገንዘብ ለሽብር ቡድን ሎጂስቲክ መግዣ ለማዋል” እንዲሁም “ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓትን በትጥቅ ትግል ለመቀየር” በመንቀሳቀስ ተጠርጥረው ለመጀመሪያ ጊዜ ፍርድ ቤት ቀረቡ።

ጉዳዩን የተመለከተው የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ የጊዜ ቀጠሮ ችሎት፤ በተጠርጣሪዎቹ ላይ 13 የምርመራ ቀናት እንደፈቀደ ጠበቃ አያሌው ቢታኔ ለቢቢሲ ተናግረዋል።

ከ10 እስከ 70 ቀናት በእስር ላይ የቆዩት ተጠርጣሪዎቹ ለመጀመሪያ ጊዜ ፍርድ ቤት የቀረቡት ትናንት ረቡዕ ግንቦት 28/2016 ዓ.ም. ከሰዓት እንደሆነ ጠበቃው አስረድተዋል።

የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ዋና መሥሪያ ቤት በሚገኘው ሦስተኛ ፖሊስ ጣቢያ ከታሰሩት ተጠርጣሪዎች ውስጥ ተዋናይ አማኑኤል ሀብታሙ ይገኝበታል። በ2006 ዓ.ም. ለዕይታ በቀረበው “ረቡኒ” ፊልም ላይ በነበረው ትወና ለመጀመሪያ ጊዜ ለዕውቅና የበቃው አርቲስት አማኑኤል፤ በተለያዩ ፊልም እና ቲያትሮች ላይ ተሳትፏል።

የአርቲስቱ የመጨረሻ ሥራ “እብደት በሕብረት” የተሰኘው ባለአንድ ሰው ቴአትር ሲሆን ሚያዝያ 14/2016 ዓ.ም. በቁጥጥር ስር የዋለውም ይህንኑ ሥራውን በእስራኤል ሀገር ለማቅረብ ሊጓዝ በነበረበት ወቅት ቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ነው።

የዚሁ ቴአትር አዘጋጅ ዳግማዊ ፈይሳ ደግሞ ከሁለት ሳምንት ገደማ በፊት በተመሳሳይ በፖሊስ ቁጥጥር ስር ውሏል። አንጋፋ የኪነ ጥበብ ባለሙያ ዳግማዊ፤ ለዕይታ ካበቃቸው ሥራዎቹ ውስጥ “የቃቄ ውርድወት” እንዲሁም አርቲስት አማኑኤል የተወነበት “የኮከቡ ሰው” የተሰኙት ቴአትሮች ተጠቃሽ ናቸው።

20 individuals, including artist Emmanuel Habtamu, theater producer Fayisa II, and the popular social media icon, Amasa Abraham, appeared in court for the first time on suspicion of “spending money for terrorist group logistics” and “changing the constitutional system through armed struggle.”

Arada Division of the Federal Court of First Instance that dealt with the case; Lawyer Ayalew Bitane told the BBC that he allowed 13 days of investigation on the suspects.

The suspects, who have been in prison for 10 to 70 days, appeared in court for the first time yesterday, Wednesday, May 28/2016. The lawyer explained that it was afternoon.

Actor Emmanuel Habtamu is one of the suspects arrested at the Third Police Station, which is the headquarters of the Addis Ababa Police Commission. In 2006 Emanuel, the artist who was recognized for the first time for his acting in the movie “Rebuni” that was presented to the public; He has acted in various films and plays.

The artist’s last work was a one-man theater called “Madness together” and was released on April 14/2016. He was arrested at Bole International Airport when he was about to travel to Israel to provide the same job.

Fayisa II, the producer of the same theater, was also detained by the police about two weeks ago. Veteran Artist II; Among his works that have ended up on display are the plays called “Kakeke Werdut” and “The Star Man” starring artist Emmanuel.

Design a site like this with WordPress.com
Get started