ጊዜያዊ አስተዳደሩ ባለፈው ሳምንት በመንግሥት ኮሚዩኒኬሽን በኩል የአከራካሪ ቦታዎችን ሁኔታ በዘላቂነት ለመፍታት “ሕዝበ ውሳኔ እንዲደረግ ከአማራ እና ከትግራይ ክልሎች ጋር መግባባት ላይ ተደርሶ ነበር” ማለቱን በመጥቀስ ነው፤ “ፍጹም የተሳሳተ [ነው]” ሲል አስተባብሏል።
የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ዛሬ ሰኞ ጥር 27/2016 ዓ.ም. አመሻሽ ላይ ባወጣው መግለጫ ሕዝበ ውሳኔውን እና ሌሎች ጉዳዮችን በማንሳት ምላሽ ሰጥቷል።
የመንግሥት ኮሚዩኒኬሽን አገልግሎት ባለፈው ሳምንት ሐሙስ ጥር 23/2016 ዓ.ም. ባወጣው መግለጫ ከፕሪቶሪያው ስምምነት በኋላ በፌደራል መንግሥት በኩል ለትግራይ ክልል ተደረገ ያለውን የበጀት እና ሌሎች ድጋፎችን በዝርዝር አስፍሯል።
የተፈናቃዮች እና የይገባኛል ጥያቄ ስለሚነሳባቸው አካባቢዎች የጠቀሰው የኮሚዩኒኬሽን አገልግሎት መግለጫ “የአከራካሪ ቦታዎችን ሁኔታ በዘላቂነት ለመፍታትም በሕገ መንግሥቱ መሠረት ሕዝበ ውሳኔ እንዲደረግ ጉዳዩ በዋናነት ከሚመለከታቸው ከአማራ እና ከትግራይ ክልሎች ጋር መግባባት ተደርሶ ነበር” ሲል አትቷል።
He denied that the interim administration of Tigray region had reached an agreement to resolve the disputed areas with the Amhara region through popular decision.
Referring to the fact that last week, the interim administration said through government communication that “an agreement was reached with the Amhara and Tigray regions for a referendum to be held to permanently resolve the situation of the disputed areas”. “It [is] completely wrong,” he denied.
The temporary administration of Tigray region today, Monday, January 27/2016. In a statement issued in the evening, he responded by raising the referendum and other issues.
Government Communication Service last week, Thursday, January 23/2016. In his statement, he detailed the budget and other support given to the Tigray region by the federal government after the Pretoria agreement.
The statement of the communication service, which mentioned about the areas where the displaced persons and claims are raised, said that “a consensus was reached with the Amhara and Tigray regions, which are mainly concerned with the issue, that a referendum should be held in accordance with the constitution to permanently resolve the situation of the disputed areas.”


Leave a comment